top of page

ዓመታዊ የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓልና የሕንፃ ቤተ ክርስቲያን የምርቃት ፕሮግራም


"እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን ደስም አለን።" መዝሙር 125 ቁ. 3


ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ፤


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሐሚልተን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ሐምሌ 7 ቀን የሚከበረውን የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በዘንድሮው ዓመትም እሁድ ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም (July 16, 2023) በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ይውላል። ከዚሁ ክብረ በዓል ጋር አብሮ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ የምርቃት ፕሮግራም ስለሚከናወን በእለቱ ተገኝታችሁ በዓሉን እንድታከብሩና የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።


ቀን (date) ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም

July 16, 2023


አድራሻ (address)

420 Aberdeen Avenue

Hamilton, ON L8P 2R5

bottom of page